በኢትዮጵያ የቴክኖሎጅና የስልጣኔ ታሪክ ዉስጥ ልዩ ቦታ በሚሰጠዉና ሁሌም የትዉልዶች ኩራት በሆነው የቅዱስ ላሊበላ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያን ድንቅ የዲዛይንን ጥበብ በሚያንጸባርቀው ቀደምት የአለም የቴክኖሎጂ ፈርጥ በሆነዉ ላሊበላ ቤተ-ክርስቲያን ልዩ የታሪክ የጥበብ ቅርስ የረጅም ጊዜ ራዕይ አንግቦና ስያሜዉን አግኝቶ በጋፋት ኢንዶውመንት እና በመቅደላ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ የአክሲዮን ሸር እ.ኤ.አ በ2016 የተቋቋመ የልማት ድርጅት ነዉ፡፡
እ.ኤ.አ በ2030 በምህንድስና፣ በማህበራዊና ኢኮኖሚ ዘርፍ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ስራዎች በምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ደረጃ በጥራት እና በብቃት ተወዳዳሪና ተመራጭ ኩባንያ ለመሆን የረጅም ራዕይ በመያዝ በመጠጥ ውሃ፣ በመስኖ፣ በህንጻ፣ በመንገድ፣ በሃይድሮጅኦሎጅ፣ በፕሮጀክትና አካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ የጥናት፣ ዲዛይን እና የግንባታ ቁጥጥር ስራዎችን በመስራት ተሳትፎውን በማሳደግ ውጤታማና በስነ-ምግባር እንዲሁም በክህሎት የተካነ አመራርና ሰራተኛ ሃይል በማቀናጀት ለጋራ ራዕይ እንዲሰለፍ በሚያስችል አግባብ እንዲደራጅ በማድረግ ተቋሙ በጥራትና በብቃት የማማከር አገልገሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡